Entries by tc

ቤተ ክርስቲያናችን መንበረ ፕትርክናው ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ ስር በአስተዳደራዊ መዋቅር መታቀፏን ስለማሳዎቅ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅድመ ታሪኩ እ.ኤ.አ በ1995 መጨረሻ ላይ ለትምህርት ወደ ትሮንዳሄም፣ ኖርዌይ በመጡ ቀናኢ የቤተክርስቲያን ልጆች አማካኝነት በሰንበት ትምህርት ቤትነት ደረጃ በመቋቋም ነበር። ሰንበት ት/ቤት በነበረበት ወቅት እ.ኤ.አ በ2010 ህጋዊ ሆኖ በኖርዌይ ሀገር በሃይማኖት ተቋምነት የተመዘገበ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ በመባል እ.ኤ.አ በ2012 በአቅራቢያው እየመጡ በሚያገለግሉን አባቶች ተሰይሟል። እ.ኤ.አ በ2013 ደግሞ ታቦተ […]

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በትሮንዳሄም ተከታታይ መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሄደ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሄም ለተከታታይ ሁለት ሳምንታት፤ ህዳር 18-19/2008ዓ.ም (November 28-29, 2015) እና ህዳር 25-26/ 2008ዓ.ም (December 05-06/2015) ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ በትሮንዳሄምና በአካባቢው የሚገኙ ምዕመናን በተገኙበት ተካሄደ። በጉባኤው መጀመርያ ቀን ቅዳሜ ህዳር 18 በአባታችን መልዓከ ሃይል መምህር አባ ዘድንግል (በጣልያን ባሪ ከተማበሚገኘው በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ) እና በዲ/ን ዶ/ር […]

የ፳፻፰ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የ ፳፻፰ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ከኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመጡ ካህናት እና መዘምራን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፣ ከትሮንዳሔምና አካባቢው በተገኙ በርካታ ምእመናን እሁድ መስከረም ፲፮ በታላቅ ድምቀት ተከበረ። በዓሉ እሁድ እለት ከሰዓት በኋላ በካህናት አባቶች ጸሎት የተጀመረ ሲሆን የቅዱስ ጊዮርጊስ […]

የ፫ ቀናት መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሄደ፤ የ፳፻፰ ዓ.ም ቅዱስ ዮሐንስ በዓልም በድምቀት ተከበረ

በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። መዝ ፷፭፥፲፩ እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ። የቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በትሮንዳሔም ከጷግሜ ፮፥፳፻፯ ዓ.ም እስከ መስከረም ፪፥፳፻፰ ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት የቆየ መንፈሳዊ ጉባኤና የአዲስ ዓመት ክብረ በዓል ከኢትዮጵያ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተጋብዘው ወደ አውሮፓ በመጡት መምህር (ቀሲስ) […]

የሊቀ ሰማዕታቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የሚያዝያ ፳፫፣ ፳፻፯ ዓ.ም የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ከተለያዩ አውሮፓ ሀገራት ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ተጋብዘው በመጡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፣ ከመላው ኖርዌይ እንዲሁም ከትሮንዳሔምና አካባቢው በተገኙ ምእመናን ዓርብ ሚያዚያ ፳፫ እና ቅዳሜ ሚያዚያ ፳፬ በታላቅ ድምቀት ተከበረ። በዓሉ ዓርብ እለት ከሰዓት በኋላ በጸሎት […]

ሊቀ-ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ

በወንድም ይበልጣል ጋሹ የቅዱስ ጊዮርጊስ አባት አንስጣስዮስ ከሮም ወደ ፍልስጤም በፈቃደ እግዚአብሔር ሄደ።በዚያም ከክቡራን መኳንንት፣ ከታላላቆች መሳፍንት መካከል አንዱ ነበር። ከፍልስጤም ዕጻ ከምትሆን ድያስ ከተባለች አገር ቴዎብስታ (አቅሌስያ) የምትባል ደግ ሚስት አገባ። የቴዎብስታ የስሟ ትርጓሜ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው። አቅሌስያም እንደ ስሟ የተቀደሰች፣ የተመሰገነች፣ የተባረከች፣ የተመረጠች በብርሃኑ ዓለምን ሁሉ ያበራውን የሰማዕታትን ኮከብ ይሸከም ዘንድ እግዚአብሔር […]

በትሮንዳሄም የ፳፻፯ ዓ.ም. የስቅለትና የትንሣኤ በዓላት አከባበር

ክርስቶስ ተንስአ እሙታን…….በዐብይ ኃይል ወስልጣን አሰሮ ለሰይጣን ………….አግአዞ ለአዳም ሰላም…………እምይእዜሰ ኮነ …………….ፍስሀ ወሰላም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለትና ትንሣኤ በትሮንዳሄም ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ። ዕለታቱን በአባ ገብረ ማሪያም ቢምረው እና በቀሲስ ካሳዬ አንተነህ የትሮንዳሄም አጥቢያና አካባቢው ምእመናን በተገኙበት ዓርብ ስቅለትን በስግደት እንዲሁም ቅዳሜ ሌሊት ደግሞ የትንሣኤን በዓል በቅዳሴ፣ በወረብና […]

በትሮንዳሄም የሆሳዕና በዓል በድምቀት ተከበረ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሄም የሆሳዕና በዓል መጋቢት ፳፯፥፳፻፯ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ። መርሃ ግብሩ በጸሎት ተጀምሮ በህጻናትና በአጥቢያው መዘምራን በዓሉን የተመለከተ ያሬዳዊ ዝማሬ ከቀረበ በኋላ የዕለቱ ትምህርተ ወንጌል በቀሲስ ወንድወሰን ተሰጥቷል።በመጨረሻም ቀጣዩ ሳምንት “ሰሙነ ህማማት” በመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት መሠረት ለምእመናን ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎ የዕለቱ መርሃ ግብር በጸሎት ተፈጽሟል፡፡ የበዓሉን አከባበር በፎቶ […]

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረ ዘይት በዓል በድምቀት ተከበረ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረ ዘይት በዓልን ከመጋቢት ፭ እስከ ፮፥ ፳፻፯ ዓ.ም. ከተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት በመጡ አባቶች ካህናት እና ወንድሞች ዲያቆናት እንዲሁም በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናን ጋር በቅዳሴ፣ በስብከተ ወንጌልና በያሬዳዊ ዝማሬ በድምቀት ተከብሯል። በዚህ በዓል ላይ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የእረፍት ቀንም ታስቦ ውሏል። በበዓሉም ላይ በመልዓከ ጽዮን […]

የ፳፻፯ ዓ.ም. የልደት በዓል አከባበር

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም አጥቢያ በሚገኙ ምእመናን እና ምእመናት በዓሉ በቅዳሴ፣ በዝማሬና በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ተከብሮ ዋለ። የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ