በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ እኛ
  • የፎቶ ማኅደሮች
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ጸሎተ ሐሙስ

ጸሎተ ሐሙስ ክርስቶስ አምላካችን ራሱን ዝቅ አድርጎ የሐዋርያትን እግር ያጠበበት ዕለት ነው፡፡

በሕማማት ውስጥ ያለው ይህ ሐሙስ በተለያዩ ስያሜዎች ይጠራል፡፡

አንደኛ፦ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኀብስቱን በባረከ ጊዜ ስለጸለየ፤  እና  ከመያዙ አስቀድሞ በጌቴሴማኒ  ደቀ መዛሙርቱ ተኝተው እርሱ ግን  ተንበርክኮ  አባት ሆይ ብትወድስ ይች ጽዋ ከእኔ ትለፍ እያለ በሰው ልጆች  (በአዳም ልጆች) ተገብት ጸልዮልናል ፡፡
ሁለተኛው፦ትዕዛዝ ሐሙስ ይባላል ፡ ምክንያቱም ከኀጽበተ እግር በኋላ ጌታ እናንተም እንዲሁ አድርጉ ብሎ  አዝዟቸዋልና ነው ከዚያም ቀጥሎ በጌቴሴማኒም  ጌታ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ ብሎ አዝዟቸዋል፤
ሦስተኛ፦ የምሥጢር ቀን ይባላል ፡ ሥርዓተ ቁርባንን ከሠራ በኋላ /ከመዝ ግብሩ ተዝካርየ/ ብሎ አዝዟል  እንዲሁም በዚህ ዕለት የተሰጡትን ሌሎችንም ትዕዛዛት ለማስታወስ ነው፡፡
አራተኛ፦ ኀጽበተ እግር  ሐሙስ ይባላል፡፡ ምክንያቱም በዚህ ቀን ጌታ የደቀመዛሙርቱን እግር ስላጠበ ባዘዘንም መሠረት ዛሬ በቤተክርስቲያን መታሰቢያውን እናደርጋለን ፡፡
አምስተኛ፦የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡፡ በዚሁ ቀን ምሽት ጌታችን ‹‹ ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፡— እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው» አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፡— ‹‹ ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።» (ማቴ.26:28) በማለት የሰጠንን ዘለዓለማዊ ኪዳን የሚያስታውስ ስያሜ ነው፡፡

ጌታችን ተጠምቆ ተጠመቁ ፣ ጾሞም ጹሙ እንዳለን ፣ ጸልዮ ጸልዩ፤ ሰግዶም ስገዱ ሲለን እንደዚሁም የደቀመዛሙርቱን እግር አጥቦ እናንተም እንዲህ አድርጉ ብሎ አርአያነቱን ሲያሳየን መምህረ ትሕትናነቱን ሲገልጥልን ነው፡፡ ዛሬም ከፓትርያርኩ ጀምሮ ሊቃነ ጳጳሳቱና ካህናቱ ሁሉም በየመዓርጋቸው የምእመናኑን እግር ዝቅ ብለው የሚያጥቡት የጌታን የትሕትና ሥራ ለማሰብ ነው፡፡

በዚህም መሠረት ይህንን ሥርዓቱን አብነት በማድረግ በዚች ቀን ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን የሕፅበተ እግር ሥርዓቱ በሚከናወንበት ጊዜ ዲያቆኑ ውኃን ያቀርባል፤ በቀረበውም ውኃ ላይ ጸሎተ አኰቴት ይጸለያል፡፡ ወንጌል ተነብቦ ውኃው በካህኑ ወይም በሊቀ ጳጳሱ እጅ ይባረክና የሕጽበተ እግር ሥርዓቱ ከካህናት እስከ አናጕንስጢስ እንደዚሁም ከወንዶች እስከ ሴቶች ላሉት ምእመናን ሁሉ በካህናቱ እጅ ይከናወናል፡፡

ከበዓሉ በረከት  ያድለን አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/tselote_hamus.jpg 251 201 Tesfaye Zerihun https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg Tesfaye Zerihun2025-04-19 19:07:172025-04-19 19:09:04ጸሎተ ሐሙስ
Search Search

በቅርብ ግዜ የተለቀቁ

  • የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ
  • ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል (ህዳር) 2025
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም.
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም. — ፎቶ
  • አዲስ አመት – ፳፻፲፰ ዓ.ም.

በፌስቡክ ያግኙን

© ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም, St. George EOTC Trondheim , በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ
ኢሜይል | አጥቢያ ፖርታል
Link to: ሆሣዕና Link to: ሆሣዕና ሆሣዕና Link to: ትንሣኤ Link to: ትንሣኤ ትንሣኤ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top