የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል

TSGC-KibreBealMastawekia 7በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
 
የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል ግንቦት ፭ እና ፮ በትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ይከበራል።
የ፳፻፰ ዓ.ም. የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል ከጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ ጋር በመግጠሙ ከአባቶች ጋር በመነጋገር በተወሰነው መሰረት ክብረ በዓሉ ዓርብ ግንቦት ፭ እና ቅዳሜ ግንቦት ፮ ፣ ፳፻፰ ዓ.ም. ለማክበር ታቅዷል። 
በበዓሉ ላይ በርካታ የቤተክርስቲያን አባቶች ከተለያዩ የአውሮጳ ሀገራት እና ከሀገረ ኖርዌይ እንዲሁም መጋቤ ሐዲስ ምስጢረ ሥላሴ ማናዬ ከኢትዮጵያ እንደሚገኙ ይጠበቃል። ከዚህ በተጨማሪም ከመላው ኖርዌይ በሚሰባሰቡ ምዕመናን፣ የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አባላት እና የቅዱስ ሚካኤል የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባቶች/ወንድሞች/እህቶች በተገኙበት በአንድነት በዓሉ በትሮንዳሔም በደማቅ ሁኔታ ይከበራል።
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን፤ አሜን።