የ፳፻፰ ዓ.ም የልደት በዓል በድምቀት ተከበረ

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም አጥቢያ በሚገኙ ምእመናን በደመቀ ሥርዓት በቅዳሴ፣ በዝማሬና በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ተከብሮ ዋለ።

እሁድ ጥር ፩፥፳፻፰ በተጋበዙ አባቶችና ዲያቆናት በኪዳንና ቅዳሴ የተጀመረው መርሐ ግብር በአጥቢያው መዘምራን በዓሉን የሚያወድሱ ያሬዳዊ ዝማሬዎች በማቅረብ የቀጠለ ሲሆን በመጨረሻም የዕለቱ ስብከተ ወንጌል በአባቶች ተሰጥቶ ቅዳሴው ተፈጽሟል። ምእመናንም ለበዓሉ የተዘጋጀውን ዝክር ቀምሰው ወደየመጡበት በሰላም ተሸኝተዋል።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ!