በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረ ዘይት በዓል በድምቀት ተከበረ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፰ ዓም የደብረ ዘይት በዓልን በቅዳሴ፣ በስብከተ ወንጌል እና በያሬዳዊ ዝማሬ ከስቶክሆልም ስዊድን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አባ ገብረ ጊዮርጊስ ካሣዬን በመጋበዝ፤ በትሮንዳሄምና አካባቢው የሚገኙ ኦርቶዶክሳዊያን ምዕመናን በተገኙበት በዓሉ በድምቀት ተከብሯል።

በዓሉ በመካከለኛው አውሮፓ የስዓት አቆጣጠር ከንጋቱ 06:00 ሰዓት በጸሎት ተጀምሮ በዓሉን የሚያወሱ ከቅዱሳት መጽሃፍት በመነበብ የኪዳንና የቅዳሴ መርሃ ግብር ተካሂዷል። ከሥርዓተ ቅዳሴው በኋላ እለቱን የተመለከቱ የንስሃ መዝሙራት በአጥቢያው መዘምራን ቀርቧል። በመቀጠልም የደብረ ዘይት በዓልን በተመለከተ ሰፋ ያለ ትምህርት በመልአከ ብርሃን አባ ገብረ ጊዮርጊስ ቀረቦ የእለቱ መርሐ ግብር በአባታችን የማሳረጊያ ጸሎት ተፈጽሟል።

በመጨረሻም በመርሃ ግብሩ የተሳተፈው ምእመናን ወ ምእመናት ለበዓሉ የተዘጋጀውን ጸበል ጸዲቅ ለበረከት እየቀመሰ በሰላም ወደ ቤቱ ተሸኝቷል።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ!