Entries by tc

ገብር ኄር (መልካም አገልጋይ)

ይህ ዕለት መልካም አገልጋዮች በትጋታቸው የሚወደሱበት ሰነፍ አገልጋዮች ደግሞ በስንፍናቸው የሚወቀሱበት ዕለት ነው።

በዓለ ደብረ ዘይት

ደበረ ዘይት ትርጉሙ ፣ «ደብር » ማለት «ተራራ» ማለት ሲሆን «ዘይት» ማለት ደግሞ «የወይራ ዛፍ » ማለት ነው። ሲገናኝ «ደብረ ዘይት» ማለት የወይራ ዛፍ የሞላበት፣ የበዛበት፣ ወይም በወይራ ደን የተሸፈነ ተራራ ማለት ነው። « የወይራ ተራራ ማለት ይሆናል።

መጻጉዕ

“አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ።”ዮሐ. 5 ፥ 17

ምኵራብ

ቦአ ኢየሱስ ምኵራበ አይሁድ፤ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት፤አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት፤እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው፤ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምሥያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ፤ቦአ ምኲራቦሙ ወገሠጾሙ ያርምሙ፤አንከሩ ምሕሮቶ ሞገሰ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዐ አፉሁ።

ቅድስት

“እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።” ኤፌሶን 5 ÷ 27

ዘወረደ

“ወአልቦ ዘዐርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለ እመሕያው ዘውእቱ ይነብር ውስተ ሰማይ።
ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።” ዮሐንስ 3 ÷ 13

በዓለ መስቀል

በጎልጎታ ዘደፈኑ አይሁድ ዮም ተረክበ ዕፀ መስቀል
አይሁድ በምቀኝነት በጎልጎታ የቀበሩት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕፀ ምስቀል እነሆ ዛሬ ተገኘ
(ቅዱስ ያሬድ )

ኖላዊ

ኖላዊ ማለት ‹‹እረኛ›› ወይም ‹‹ጠባቂ›› ማለት ሲሆን በዚህ ዕለት ቅዱሳን ነቢያት አምላክ ወልደ አምላክ እውነተኛ ጠባቂ ሆኖ ይገለጣል ብለው ትንቢት መናገራቸው እና ቅዱሳን ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት ኖላዊ ዘበአማን እውነተኛ ጠባቂ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ቤተክርስቲያናችን የምታስተምርበት ዕለት ነው፡፡

ብርሃን

የዘመነ ስብከት ሁለተኛው ሰንበት ‹‹ብርሃን›› ይባላል፡፡ ነቢያት የነፍሳችን ብርሃን ይወለዳል ብለው ስለመስበካቸው፣ እውነተኛ ብርሃን ይመጣል ብለው ሰለማስተማራቸው የሚታሰብበት ሲሆን በዚሁ ዕለት ኢየሱስ ክርስቶስ አማናዊ ብርሃን መሆኑ ይሰበካል፤ ይዘመራልም፡