የ፳፻፮ ዓ.ም. የስቅለትና የትንሣኤ በዓላት አከባበር

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለትና በዓለ ትንሣኤ በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም አጥቢያ በሚገኙ ምእመናን እና ምእመናት በዕለቱ ተከብሮ ዋለ።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

የ፳፻፮ ዓ.ም. ደብረዘይት በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረዘይት በዓልን ከመጋቢት ፲፪ እስከ ፲፫፣ ፳፻፮ ዓ.ም. ከተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ከመጡ አባቶች ካህናት እና ወንድሞች ዲያቆናት እንዲሁም በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምእመናትጋር በቅዳሴ፣ በስብከተ ወንጌልና በያሬዳዊ ዝማሬ በታላቅ ድምቀት አከበረ።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ ጉባኤውን አደረገ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም እሁድ ጥር ፲፰ ቀን ፳፻፮ ዓ. ም ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ። ጉባኤው በጸሎት ከተጀመረ በኋላ እ.ኤ.አ የ2013 እቅድ አፈጻጸምና የኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2014/እ.ኤ.አ/ ዕቅድ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ጸድቋል። ጉባኤው የተጀመረውን ዓመት በኃላፊነት ሊያገለግሉ የሚችሉ ሰባት መንፈሳዊ የሰበካ ጉባኤ አባላትን መርጦ ከአጸደቀ በኋላ በጸሎት ተዘግቷል።

ጠቅላላ ጉባኤው በፎቶ

የጥምቀት በዓል በኖርዌይ በድምቀት ተከበረ

በኖርዌይ በተለያዩ ከተማ የሚገኙት ስድስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናት ማለትም የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል፤ የስታቫንጋር መድኃኔዓለም፤ የክርስቲያንሳንድ ቅድስት ድንግል ማርያም፤ የበርገን እመቤታችንና ቅዱስ ሚካኤል እና የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦታት አንድ ላይ በመሆን የጌታችን የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት በበርገንበታላቅ ድምቀት አከበሩ። በዓሉ በኖርዌይና ከተለያዩ ሃገራት በመጡ አባቶች ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት መሰረት ከከተራ ጀምሮ ማለትም ጥር ፲ እና ፲፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም በደማቅ መንፈሳዊ አገልግሎት ተከበረ። የጥምቀት በዓል በኖርዌይ በአንድነት መከበር የጀመረው በ፳፻፬ ዓ.ም በኦስሎ ከተማ ሲሆን እንደዚህ ቁጥራቸው በዛ ባሉ ታቦታት ሲከበር ግን የመጀመሪያ ነው። ይህ በዓል ባለፈው ዓመትም በስታቫንገር እንደዚሁ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ እንደነበር ይታወሳል።

Read more

በትሮንዳሔም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ተቋቋመ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ቤት ከ 17 ዓመታት ጉዞ በኋላ ወደ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አደገ። ሰንበት ትምህርት ቤቱ እ.ኤ.አ በ 1995 «በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ት/ቤት» ተብሎ የተመሰረተ ሲሆን አሁን ቅዱስ እግዚአብሔር ፈቅዶ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ በሊቃነ ጳጳሳት ተባርኮ በመጋቢ ምስጢር ቆሞስ አባ ቴዎድሮስ አማካኝነት ወደ ኖርዌይ በመምጣቱ ወደ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሊያድግ ችሏል። አጥቢያ ቤተ ክርስቲያኑን ማቋቋም አስመልክቶ የሁለት ቀን ጉባኤ ታህሳስ ፬ እና ፭ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ተዘጋጅቶ ታቦተ ሕጉን በደማቅ ስነ ሥርዓት ከተቀበልን በኋላ በሥርዓተ ጸሎት በትሮንዳሔም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተቋቋመ። Read more

ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት በትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ተሰጠ

በኖርዎዌይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት ማለትም ጥቅምት ፲፯ እና ፳፬ እንዲሁም ህዳር ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ስለ ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ተከታታይ ትምህርት ለአባላት በዕለተ ሰንበት ከጸሎት በኋላ ተሰጥቷል። ተከታታይ ትምህርቱ የተዘጋጀው የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ስለ ቅዱስ ቁርባንና ቅዱስ ጋብቻ ትምህርት እንዲሰጣቸዉ በጠየቁት መሰረት ነው። ትምህርቱን የሰጠዉ ዲ/ን አብይ ከኦታ ሲሆን በትምህርቱ ወቅት አባላቱ ላቀረቡት የተለያዩ ጥያቄዎች መልሶችና ማብራሪያዎች ተሰጥተዋል።

መርሃግብሩን በፎቶ ይመልከቱ

የመስቀል በዓል አከባበር

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! በትሮንዳሔም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት የደመራ በዓልን ሐሙስ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ደመራ በማብራት እና በዝማሬ በድምቀት አከበረ። የመስቀልን በዓል ምክንያት በማድረግም በዓመታዊው መርሃ ግብራችን መሰረት ቅዳሜ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፮ዓ.ም. በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናንና ምዕመናት በተገኙበት የቅዳሴ መርሃ ግብር ተደርጓል። ዘመነ ማርቆስ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የንስሐና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። የሥላሴ ቸርነት፣ የእመቤታችን አማላጅነት፣ የመስቀሉ በረከት ይደርብን፡፡ አሜን።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!

በትሮንዳሔም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ርት ቤት የቅዱስ ዮሐንስን ዓመታዊ በዓል/ የ፳፻፮ ዓ.ም. የዘመን መለወጫን መስከረም ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በአካባቢው ከሚኖሩ ክርስቲያኖች ጋር በመሆን በዝማሬ እና በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች በድምቀት አከበረ። ዘመነ ማርቆስ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የንስሐና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን የእግዚያብሔር ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። አሜን።

ፎቶ ይመልከቱ

የደብረ ታቦር በዓልና የጠቅላላ ጉባኤ አከባበር

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የትሮንዳሔም ሰ/ት/ቤት ቀደም ብሎ በተያዘው ዓመታዊ መርሀ ግብር መሰረት የደብረ ታቦርን በዓል ከአባቶች ካህናት፣ በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምዕመናት ጋር በመሆን ነሐሴ ፲፩ ፳፻፭ ዓ.ም. በድምቀት አከበረ። በማግስቱ ነሐሴ ፲፪ ቀን ደግሞ አብላጫው የሰንበት ት/ቤቱ አባላት በተስማሙበት መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ ተደርጐ የ ፮ ወር የአገልግሎት አፈጻጸምና ኦዲት ሪፖርቶች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የደብረ ታቦር በዓልንና ጠቅላላ ጉባኤ አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

ስብከተ ወንጌልና ትምህርት በት/ሰ/ት/ቤት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት ከሀገር ቤት በመጡ መምህር ሰኔ ፳፪ እና ፳፫ ፳፻፭ ዓ.ም የስብከተ ወንጌል መርሃ ግብር በርካታ በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት ያካሄደ ሲሆን በተጨማሪም ከምዕመኑ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሾችና ማብራሪያዎች ተሰጥቷል። ሰኔ ፳፬ እና ፳፭ ደግሞ አምስቱ አዕማደ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና የስብከት ዘዴን በተመለከተ መጠነኛ ትምህርትና ስልጠና ተሰጥቷል።

መርሃግብሩን በፎቶ ይመልከቱ