በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ እኛ
  • የፎቶ ማኅደሮች
  • ያግኙን
  • Menu Menu

በትሮንዳሔም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ተቋቋመ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ቤት ከ 17 ዓመታት ጉዞ በኋላ ወደ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አደገ። ሰንበት ትምህርት ቤቱ እ.ኤ.አ በ 1995 «በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ት/ቤት» ተብሎ የተመሰረተ ሲሆን አሁን ቅዱስ እግዚአብሔር ፈቅዶ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ በሊቃነ ጳጳሳት ተባርኮ በመጋቢ ምስጢር ቆሞስ አባ ቴዎድሮስ አማካኝነት ወደ ኖርዌይ በመምጣቱ ወደ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሊያድግ ችሏል። አጥቢያ ቤተ ክርስቲያኑን ማቋቋም አስመልክቶ የሁለት ቀን ጉባኤ ታህሳስ ፬ እና ፭ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ተዘጋጅቶ ታቦተ ሕጉን በደማቅ ስነ ሥርዓት ከተቀበልን በኋላ በሥርዓተ ጸሎት በትሮንዳሔም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተቋቋመ። Read more

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-12-18 17:58:172018-10-11 14:45:14በትሮንዳሔም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ተቋቋመ

ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት በትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ተሰጠ

በኖርዎዌይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት ማለትም ጥቅምት ፲፯ እና ፳፬ እንዲሁም ህዳር ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ስለ ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ተከታታይ ትምህርት ለአባላት በዕለተ ሰንበት ከጸሎት በኋላ ተሰጥቷል። ተከታታይ ትምህርቱ የተዘጋጀው የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ስለ ቅዱስ ቁርባንና ቅዱስ ጋብቻ ትምህርት እንዲሰጣቸዉ በጠየቁት መሰረት ነው። ትምህርቱን የሰጠዉ ዲ/ን አብይ ከኦታ ሲሆን በትምህርቱ ወቅት አባላቱ ላቀረቡት የተለያዩ ጥያቄዎች መልሶችና ማብራሪያዎች ተሰጥተዋል።

መርሃግብሩን በፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-11-10 17:33:322018-10-11 14:45:14ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት በትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ተሰጠ

የመስቀል በዓል አከባበር

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! በትሮንዳሔም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት የደመራ በዓልን ሐሙስ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ደመራ በማብራት እና በዝማሬ በድምቀት አከበረ። የመስቀልን በዓል ምክንያት በማድረግም በዓመታዊው መርሃ ግብራችን መሰረት ቅዳሜ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፮ዓ.ም. በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናንና ምዕመናት በተገኙበት የቅዳሴ መርሃ ግብር ተደርጓል። ዘመነ ማርቆስ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የንስሐና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። የሥላሴ ቸርነት፣ የእመቤታችን አማላጅነት፣ የመስቀሉ በረከት ይደርብን፡፡ አሜን።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-09-29 19:22:552018-10-11 14:45:14የመስቀል በዓል አከባበር

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!

በትሮንዳሔም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ርት ቤት የቅዱስ ዮሐንስን ዓመታዊ በዓል/ የ፳፻፮ ዓ.ም. የዘመን መለወጫን መስከረም ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በአካባቢው ከሚኖሩ ክርስቲያኖች ጋር በመሆን በዝማሬ እና በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች በድምቀት አከበረ። ዘመነ ማርቆስ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የንስሐና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን የእግዚያብሔር ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። አሜን።

ፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-09-12 18:38:132018-10-11 14:45:14እንኳን ለዘመነ ማርቆስ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!

የደብረ ታቦር በዓልና የጠቅላላ ጉባኤ አከባበር

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የትሮንዳሔም ሰ/ት/ቤት ቀደም ብሎ በተያዘው ዓመታዊ መርሀ ግብር መሰረት የደብረ ታቦርን በዓል ከአባቶች ካህናት፣ በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምዕመናት ጋር በመሆን ነሐሴ ፲፩ ፳፻፭ ዓ.ም. በድምቀት አከበረ። በማግስቱ ነሐሴ ፲፪ ቀን ደግሞ አብላጫው የሰንበት ት/ቤቱ አባላት በተስማሙበት መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ ተደርጐ የ ፮ ወር የአገልግሎት አፈጻጸምና ኦዲት ሪፖርቶች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የደብረ ታቦር በዓልንና ጠቅላላ ጉባኤ አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-08-21 18:08:422018-10-11 14:45:14የደብረ ታቦር በዓልና የጠቅላላ ጉባኤ አከባበር

ስብከተ ወንጌልና ትምህርት በት/ሰ/ት/ቤት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት ከሀገር ቤት በመጡ መምህር ሰኔ ፳፪ እና ፳፫ ፳፻፭ ዓ.ም የስብከተ ወንጌል መርሃ ግብር በርካታ በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት ያካሄደ ሲሆን በተጨማሪም ከምዕመኑ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሾችና ማብራሪያዎች ተሰጥቷል። ሰኔ ፳፬ እና ፳፭ ደግሞ አምስቱ አዕማደ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና የስብከት ዘዴን በተመለከተ መጠነኛ ትምህርትና ስልጠና ተሰጥቷል።

መርሃግብሩን በፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-07-04 11:53:312018-10-11 14:45:14ስብከተ ወንጌልና ትምህርት በት/ሰ/ት/ቤት

የትንሣኤ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት የትንሣኤንና የዳግም ትንሣኤን በዓላት ሚያዚያ ፳፯ እና ግንቦት ፫ ቀን ፳፻፭ ዓ።ም ከአባቶች ካህናት እና በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት ጋር አከበረ።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-05-17 21:12:342018-10-11 14:45:14የትንሣኤ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

የደብረዘይት በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት የደብረዘይት በዓልን መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም  ከአባቶች ካህናት እና በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት ጋር በድምቀት አከበረ።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg 0 0 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2013-03-05 09:49:202018-10-11 14:45:14የደብረዘይት በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ
Page 6 of 6«‹456
Search Search

በቅርብ ግዜ የተለቀቁ

  • የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ
  • ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል (ህዳር) 2025
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም.
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም. — ፎቶ
  • አዲስ አመት – ፳፻፲፰ ዓ.ም.

በፌስቡክ ያግኙን

© ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም, St. George EOTC Trondheim , በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ
ኢሜይል | አጥቢያ ፖርታል
Scroll to top Scroll to top Scroll to top