Entries by tc

የደብረ ታቦር በዓል እና ጾመ ፍልሰታን ምክንያት በማድረግ ጉባኤ ተካሄደ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሄም የደብረ ታቦር በዓልና ጾመ ፍልሰታን ምክንያት በማድረግ ለ፪ ቀናት ማለትም ነሐሴ ፳፫ እና ፳፬ ፳፻፮ ዓ.ም የአካባቢው ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት መንፈሳዊ ጉባኤ ተካሄደ። በጉባኤውም ላይ መላከ ጽዮን ቆሞስ አባ ሙሴ በመገኘት የስብከተ ወንጌል አገልግሎትና ስርዓተ ቅዳሴ እንዲከናወን በማድረግ በዓሉ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል። ጉባኤውን በፎቶ ይመልከቱ

የ፫ ቀናት መንፈሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሄም በመምህር ምሥጢረ ሥላሴ ማናዬ ከነሐሴ ፪ እስከ ፬ ፳፻፮ ዓ.ም መንፈሳዊ ጉባኤ ተካሄደ። በጉባኤውም ላይ በአካባቢው ለሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት የሦስት ቀን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ተካፋይ እንዲሆኑ ተደርጓል። ጉባኤውም በስርዓተ ጸሎት ተጀምሮ በእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ በጸሎት ተጠናቋል። ጉባኤውን በፎቶ ይመልከቱ

የ፳፻፮ ዓ.ም. የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር የ፳፻፮ ዓ.ም. የዳግም ትንሣኤንና የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓላት ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ተጋብዘው በመጡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፣ ምእመናን እና ምእመናት በተገኙበት ዓርብ ሚያዚያ ፲፯ እና ቅዳሜ ሚያዚያ ፲፰ በታላቅ ድምቀት አከበረ። በዓሉ በማሕሌት፣ በቅዳሴ፣ በትምህርተ ወንጌልና በመዝሙር የተከበረ ሲሆን ያሬዳዊ ዝማሬም በደብሩ መዘምራን ቀርቧል። በተጨማሪም የላቫንጋርና […]

የ፳፻፮ ዓ.ም. የስቅለትና የትንሣኤ በዓላት አከባበር

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለትና በዓለ ትንሣኤ በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም አጥቢያ በሚገኙ ምእመናን እና ምእመናት በዕለቱ ተከብሮ ዋለ። የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

የ፳፻፮ ዓ.ም. ደብረዘይት በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረዘይት በዓልን ከመጋቢት ፲፪ እስከ ፲፫፣ ፳፻፮ ዓ.ም. ከተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ከመጡ አባቶች ካህናት እና ወንድሞች ዲያቆናት እንዲሁም በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምእመናትጋር በቅዳሴ፣ በስብከተ ወንጌልና በያሬዳዊ ዝማሬ በታላቅ ድምቀት አከበረ። የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ ጉባኤውን አደረገ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም እሁድ ጥር ፲፰ ቀን ፳፻፮ ዓ. ም ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ። ጉባኤው በጸሎት ከተጀመረ በኋላ እ.ኤ.አ የ2013 እቅድ አፈጻጸምና የኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2014/እ.ኤ.አ/ ዕቅድ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ጸድቋል። ጉባኤው የተጀመረውን ዓመት በኃላፊነት ሊያገለግሉ የሚችሉ ሰባት መንፈሳዊ የሰበካ ጉባኤ አባላትን መርጦ ከአጸደቀ በኋላ በጸሎት ተዘግቷል። ጠቅላላ […]

የጥምቀት በዓል በኖርዌይ በድምቀት ተከበረ

በኖርዌይ በተለያዩ ከተማ የሚገኙት ስድስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናት ማለትም የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል፤ የስታቫንጋር መድኃኔዓለም፤ የክርስቲያንሳንድ ቅድስት ድንግል ማርያም፤ የበርገን እመቤታችንና ቅዱስ ሚካኤል እና የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦታት አንድ ላይ በመሆን የጌታችን የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት በበርገንበታላቅ ድምቀት አከበሩ። በዓሉ በኖርዌይና ከተለያዩ ሃገራት በመጡ አባቶች ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት መሰረት […]

በትሮንዳሔም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ተቋቋመ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ቤት ከ 17 ዓመታት ጉዞ በኋላ ወደ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አደገ። ሰንበት ትምህርት ቤቱ እ.ኤ.አ በ 1995 «በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ት/ቤት» ተብሎ የተመሰረተ ሲሆን አሁን ቅዱስ እግዚአብሔር ፈቅዶ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ በሊቃነ ጳጳሳት ተባርኮ በመጋቢ ምስጢር ቆሞስ አባ ቴዎድሮስ አማካኝነት ወደ […]

ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት በትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ተሰጠ

በኖርዎዌይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት ማለትም ጥቅምት ፲፯ እና ፳፬ እንዲሁም ህዳር ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ስለ ሰባቱ ምስጢራተ-ቤተክርስቲያን ተከታታይ ትምህርት ለአባላት በዕለተ ሰንበት ከጸሎት በኋላ ተሰጥቷል። ተከታታይ ትምህርቱ የተዘጋጀው የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ስለ ቅዱስ ቁርባንና ቅዱስ ጋብቻ ትምህርት እንዲሰጣቸዉ በጠየቁት መሰረት ነው። ትምህርቱን የሰጠዉ […]

የመስቀል በዓል አከባበር

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! በትሮንዳሔም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት የደመራ በዓልን ሐሙስ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ደመራ በማብራት እና በዝማሬ በድምቀት አከበረ። የመስቀልን በዓል ምክንያት በማድረግም በዓመታዊው መርሃ ግብራችን መሰረት ቅዳሜ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፮ዓ.ም. በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናንና ምዕመናት በተገኙበት የቅዳሴ መርሃ ግብር ተደርጓል። ዘመነ ማርቆስ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የንስሐና […]