በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ እኛ
  • የፎቶ ማኅደሮች
  • ያግኙን
  • Menu Menu

እንኩዋን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

”እነሆ ለህዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምስራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና…..”ሉቃ.2፤11

አስቀድሜ እንኩዋን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ፡፡

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ለሰው ልጆች ሁሉ መልካም ዜና ነው፡፡እርሱ የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ለማስወገድ ተወለደ፡፡መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደ ነገራት ”….ስሙን ኢየሱስ ትዪዋለሽ እርሱም ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል..” የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ቀ. 32 ፡፡

ምናልባት ብዙ ጊዜ በተለምዶ ብቻ ገናን ወይም ልደትን ማክበር እየተስፋፋ የሄደ ጉዳይ ነው፡፡ ፈረንጆቹ በልደቱ ቀን ስጦታን መለዋወጥ ፤ ዛፎችን በደመቀ መብራት ማሸብረቅ፤ መብላት እና መጠጣት የመሳሰሉትን ጉዳዮች በመፈጸም ቀኑን ያሳልፋሉ፡፡ከበዛ ደግሞ ሳንታ ክሎስ ብለው ከሰየሙት የገና አባት ጋር ፎቶ መነሳት ሕጻናትን በውሸት ትርክት እንዲደነዝዙ በማድረግ የልደቱን ነገር የሚሸፍኑበትን የገና አባት የውሸት ትርክት እየነገሩ በማታለል….የልጆችን እውነቱን የማወቅ መብት በጊዜአዊ ብልጭልጭ ስጦታ ቀይረውታል፡፡
እንዲያውም አሁን አሁን ገና ማለት የልጆች ቀን ክፍለ ጊዜ እየመሰለ መጥቷል ፡፡ይህ ማለት ከዋናው ጉዳይ ጋር በእጅጉ የሰማይና የምድር ያህል እየተራራቅንና እየተለያየን ነው ማለት ነው፡፡

በአገራችንም ከዚህ ባልተናነሰ ሁኔታ ባህላዊ ምግቦችን በማዘጋጀት እና የገና ዛፎችን በማስጌጥ ሲዘፈን ሲጨፈር መዋል የተለመደ ነገር ሁኗል፡፡
ብቻ በሁሉም ጎን ማለት ይቻላል ፈር የለቀቀ ጉዳይ ይስተዋላል፡፡ ማለትም ከዋናው ጉዳይ ጋር ያለተገናኙ ነገሮች የበዓሉ ዋና ነገር ሆነው ቀርበዋልና፡፡

ከርስቶስን ከልደቱ ጀምሮ ሊገድለው ሲፈልግ የነበረ ሰይጣን፤ በኋላም ከሞት መነሳቱን በውሸት ዜና ተክቶ አልተነሳም ብለው እንዲናገሩ ሲጥር የነበረው ሰይጣን፤ አሁን ደግሞ ስልቱን ቀይሮ ሰዎች የልደቱን ትክክለኛ አላማ ቁም ነገር እንዳይረዱ በማድረግ በሚችለው ሁሉ እየሰራ ይገኛል፡፡በተወሰነ መልኩ የተሳካለትም ይመስላል፡፡

የልደቱን ምሥጢር ብዙዎች አልገባንም በቤተ ልሔም በግርግም የተወለደውን ሕፃን ከልባችንና ከቤት አስወጥተን ፤ በሰላሙ ፋንታ ሁከት በፍቅሩ ፋንታ ጥላቻውን በሕይወት ፋንታ ሞትን እያስፋፋን ወንድም ወንድሙን ልጅ አባቱን አባት ልጁን ወገን ወገኑን ለሞት አሳልፈን እየሰጠን።  ሰላም እምነት ደግነት የዋሀት ትሕትና ትዕግሥት እነዚህ ሁሉ ከልባችን ርቀው እነሱን ሳንመልስ ደግሞ ልደት ለማክበር ደፋ ቀና ማለት ምን ያህል ያለማስተዋል ይሆን ?
ምእመናን ሆይ ልብ ልንል የሚገባው ዋና ነገር የተወለደው ሕፃን ክርስቶስ በእኛ ልብ ስለመኖሩ እና የተወለደበት፣ የተሰቀለበት፣ የሞተበትና፣ የተነሳበት ትክክለኛ ዓላማ ገብቶናል ወይ የሚለው ቁም ነገር ነው፡፡
ተፈሥሒ ኦ ቤተ ልሔም ሀገሮሙ ለመላእክት እስመ በኀቤኪ ተወልደ ክርስቶስ ዳግማይ አዳም ከመ ያግብዖ ለአዳም ቀዳሚ ብእሲ እምድር ውስተ ገነት ፣
የመላእክት ሀገራቸው ቤተ ልሔም ሆይ ደስ ይበልሽ የቀደመ ሰው አዳምን ከምድር ወደገነት ከሞት ወደ ሕይወት ይመልሰው ዘንድ በአንች ከአንች ተወልዷልና ፤ ብሎ ቅዱስ ኤፍሬም እንዳመሰገነ እኛም ገብቶንና ተረድተነው ልናከብር ልናመሰግን ይገባል።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከኃጢአት ለማዳን ተወለደ፤በእርሱ የኃጢአታችንን ስርየት እናገኛለን /የሐዋርያት ሥራ.10፤43/፤
መጽሐፍ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላል፡፡ ሮሜ 10፤11

እርሱ የሕይወታችንም የክርስትናችንም መሠረት ነው፡፡ ያውም በልደቱ ቀን እርሱን ደስ የማያሰኘውን ጉዳይ እየፈጸምን እርሱን ከቤታችንና ከልባችን አስወጥተን ሰደን ወይም ቸል ብለን ድግሱ ላይ ብቻ የምናተኩር ከሆንን ምኑ ላይ ነው ክርስትናው? ያስብላል፤

ስለዚህ እግዚአብሔር ሆይ አንድያ ልጅህን ወደ ዓለም ልከህ ስለ ዓለም ሁሉ ኃጢአት ቤዛ እንዲሆን ፈቃድህ ስለ ሆነ እናመሰግንሃለን ፡ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሰራነውን መተላለፍና ኃጢአት ይቅር በለን፡፡
ጌታ ሆይ ወደ ልባችን እንድትመልሰን እንማፀናለን ሁለጊዜ አንተን በማመን ጸንተን እንድንኖር እርዳን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ፍቅር ከሁላችን ጋር ይሁን በዓሉን የበረከት የንስሐ የሥርየት በዓል ያድርግል ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን። ይቆየን።

መልካም በዓል ያድርግልን

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/lidet-13-cover.jpg 406 400 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2024-01-06 09:01:192024-01-06 09:01:19እንኩዋን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
Search Search

በቅርብ ግዜ የተለቀቁ

  • የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ
  • ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል (ህዳር) 2025
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም.
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም. — ፎቶ
  • አዲስ አመት – ፳፻፲፰ ዓ.ም.

በፌስቡክ ያግኙን

© ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም, St. George EOTC Trondheim , በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ
ኢሜይል | አጥቢያ ፖርታል
Link to: ኖላዊ Link to: ኖላዊ ኖላዊ Link to: ደብረ ዘይት Link to: ደብረ ዘይት ደብረ ዘይት
Scroll to top Scroll to top Scroll to top