Entries by tc

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!

በትሮንዳሔም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ርት ቤት የቅዱስ ዮሐንስን ዓመታዊ በዓል/ የ፳፻፮ ዓ.ም. የዘመን መለወጫን መስከረም ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በአካባቢው ከሚኖሩ ክርስቲያኖች ጋር በመሆን በዝማሬ እና በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች በድምቀት አከበረ። ዘመነ ማርቆስ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የንስሐና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን የእግዚያብሔር ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። አሜን። ፎቶ ይመልከቱ

የደብረ ታቦር በዓልና የጠቅላላ ጉባኤ አከባበር

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የትሮንዳሔም ሰ/ት/ቤት ቀደም ብሎ በተያዘው ዓመታዊ መርሀ ግብር መሰረት የደብረ ታቦርን በዓል ከአባቶች ካህናት፣ በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምዕመናት ጋር በመሆን ነሐሴ ፲፩ ፳፻፭ ዓ.ም. በድምቀት አከበረ። በማግስቱ ነሐሴ ፲፪ ቀን ደግሞ አብላጫው የሰንበት ት/ቤቱ አባላት በተስማሙበት መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ ተደርጐ የ ፮ ወር የአገልግሎት አፈጻጸምና ኦዲት ሪፖርቶች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ተደርጎባቸዋል። […]

ስብከተ ወንጌልና ትምህርት በት/ሰ/ት/ቤት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት ከሀገር ቤት በመጡ መምህር ሰኔ ፳፪ እና ፳፫ ፳፻፭ ዓ.ም የስብከተ ወንጌል መርሃ ግብር በርካታ በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት ያካሄደ ሲሆን በተጨማሪም ከምዕመኑ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሾችና ማብራሪያዎች ተሰጥቷል። ሰኔ ፳፬ እና ፳፭ ደግሞ አምስቱ አዕማደ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና የስብከት ዘዴን በተመለከተ መጠነኛ ትምህርትና ስልጠና ተሰጥቷል። መርሃግብሩን […]

የትንሣኤ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት የትንሣኤንና የዳግም ትንሣኤን በዓላት ሚያዚያ ፳፯ እና ግንቦት ፫ ቀን ፳፻፭ ዓ።ም ከአባቶች ካህናት እና በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት ጋር አከበረ። የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

እናመሰግናለን

ለሰጡን አስተያየት እናመሰግናለን። አስተያየትዎት ምላሽ የሚያሻ ከሆነ በተቻለን መጠን ምላሽ ለመስጠት እንሞክራለን። ቅዱስ እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይባርክ!!!

ትምህርታዊ ጽሑፎች

ትምህርተ ሃይማኖት ትምህርተ ሃይማኖት – ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል ትምህርተ ሃይማኖት – ማኅበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማዕከል ልዩ ልዩ ሊቀ-ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብረ ዘይት “መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡- መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው” /መዝ.86፥1/ “የትንሣኤው ትርጉም በዓሉና አከባበሩ” “ፍኖተ መስቀል” ሰሙነ ሕማማት “ወደጄ ሆይ ተነሺ፣ ውበቴ ሆይ ነይ” (መኃ 2፡10) መንፈሳዊ ሕይወትና ስደት

ስለ እኛ

ታሪክ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  የትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መነሻው እ.ኤ.አ በ1995 መጨረሻ ላይ ለትምህርት ወደ ኖርዌይ ትሮንዳሔም በመጡ የቤተክርስቲያን ፍቅር ባላቸው ተማሪዎች አማካኝነት የተመሰረተ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። ሰንበት ት/ቤቱ በተለያዩ መዋቅሮች ተደራጅቶ አገልግሎቱን አጠናክሮ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ትሮንዳሔም ለመጡ የእምነቱ ተከታዮች አገልግሎት ዘወትር እሁድ የፀሎት መርሐግብር እንዲሁም በአበይት በዓላት ጊዜ የቅዳሴ አገልግሎት […]

Educational Material

This section shows educational materials of the EOTC select from the right menu what you want . . .

የደብረዘይት በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የትሮንዳሔም ሰንበት ትምህርት ቤት የደብረዘይት በዓልን መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም  ከአባቶች ካህናት እና በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናንና ምእመናት ጋር በድምቀት አከበረ። የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ