በትሮንዳሄም የሆሳዕና በዓል በድምቀት ተከበረ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሄም የሆሳዕና በዓል መጋቢት ፳፯፥፳፻፯ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ። መርሃ ግብሩ በጸሎት ተጀምሮ በህጻናትና በአጥቢያው መዘምራን በዓሉን የተመለከተ ያሬዳዊ ዝማሬ ከቀረበ በኋላ የዕለቱ ትምህርተ ወንጌል በቀሲስ ወንድወሰን ተሰጥቷል።በመጨረሻም ቀጣዩ ሳምንት “ሰሙነ ህማማት” በመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት መሠረት ለምእመናን ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎ የዕለቱ መርሃ ግብር በጸሎት ተፈጽሟል፡፡

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ