በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረ ዘይት በዓል በድምቀት ተከበረ

በቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም የደብረ ዘይት በዓልን ከመጋቢት ፭ እስከ ፮፥ ፳፻፯ ዓ.ም. ከተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት በመጡ አባቶች ካህናት እና ወንድሞች ዲያቆናት እንዲሁም በአካባቢው ከሚኖሩ ምእመናን ጋር በቅዳሴ፣ በስብከተ ወንጌልና በያሬዳዊ ዝማሬ በድምቀት ተከብሯል። በዚህ በዓል ላይ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የእረፍት ቀንም ታስቦ ውሏል። በበዓሉም ላይ በመልዓከ ጽዮን ቆሞስ አባ ሙሴና በዲያቆን ዓብይ በዓሉን በሚመለከት ትምህርተ ወንጌል በሰፊው ተሰጧል።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ