በትሮንዳሄም የ፳፻፯ ዓ.ም. የስቅለትና የትንሣኤ በዓላት አከባበር

ክርስቶስ ተንስአ እሙታን…….በዐብይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን ………….አግአዞ ለአዳም
ሰላም…………እምይእዜሰ
ኮነ …………….ፍስሀ ወሰላም
የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለትና ትንሣኤ በትሮንዳሄም ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ። ዕለታቱን በአባ ገብረ ማሪያም ቢምረው እና በቀሲስ ካሳዬ አንተነህ የትሮንዳሄም አጥቢያና አካባቢው ምእመናን በተገኙበት ዓርብ ስቅለትን በስግደት እንዲሁም ቅዳሜ ሌሊት ደግሞ የትንሣኤን በዓል በቅዳሴ፣ በወረብና በዝማሬ በድምቀት ተከብሯል።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ