የ፳፻፰ ዓ.ም የፍልሰታ ለማርያም ጾም አጋማሽ ቅዳሴና የአንድ ቀን ጉባኤ ተካሄደ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሀ/ስብከት የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ቅዳሜ ነሐሴ ፯፥፳፻፰ ዓ.ም ከኢትዮጵያ በመጡት ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ (ሊቀ መዘምር) የፍልሰታን ጾም በማስመልከት የቅዳሴ መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን ከቅዳሴው በኋላ በአጥቢያው ሕጻናት አጫጭር መዝሙራት ቀርበዋል። ። በመቀጠልም በቀሲስ ምንዳዬ ዝማሬዎችና ዕለቱን የተመለከተ የወንጌል ትምህርት ተሰጥቷል። በመጨረሻም የዕለቱ መርሐ ግብር በአባታችን ቡራኬ ተፈጽሟል።

በነጋታው እሁድ ነሐሴ ፰፥ ዓ.ም ረፋድ ላይ የዕለቱ መርሐ ግብር ኪዳን በማድረስ የተጀመረ ሲሆን በመቀጠልም ቀሲስ ምንዳዬ ተከታታይ ዝማሬዎችን ካቀረቡ በኋላ የዕለቱ የወንጌል ትምህርት በወንድም ኃይሉ (ዶ/ር) ስለጾም አስፈላጊነት ሰፋ ያለ ትምህርት ተሰጥቷል። በስተመጨረሻም በቀሲስ ምንዳዬ የማጠቃለያ ትምህርትና ተጨማሪ ዝማሬዎች ተዘምረው የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት ተፈጽሟል። በዕለቱ የተገኙት ምዕመናንም ከቀሲስ ምንዳዬ ጋር የማስታወሻ ፎቶ ተነስተው በዕለቱ የተዘጋጀውን ጸበል ጸዲቅ ቀምሰው ወደየቤታቸው በሰላም ተመልሰዋል።

መርሐ ግብሩን በምስል ይመልከቱ !