በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ እኛ
  • የፎቶ ማኅደሮች
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ትንሣኤ

“እንደተናገረ ተነስቷል።” ማቴ  28 ፥ 6
ትንሣኤ ማለት ቀጥታ የቃሉ ትርጉም መነሣት ማለት ነው።

ብዙዎቻችንም እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን አደረሳችሁ እያልን እና እየተባባልን  ነው። ፖለቲከኛውም፣ ሰባኪውም፣ ጳጳሱም፣ ዘማሪውም  ዘፋኙም፣  አርቲስቱም፣ አክቲቪስቱም ሁሉም እንኳን አደረሳችሁ እያለ ነው። ጥሩ ነው ፥ ለምን ይባላል ማለት አይገባም ፥ ደስ ይላል ፥ መጠያየቁ  መተሳሰቡ ከልብ ከሆነ !! በሌላ መልኩ መድረስ የሚለው ቃል ናፋቂ ሆኗል ፥ ውሎ መግባት ፣ አድሮ  መገኘት ፣ ተኝቶ መነሳት ፣ ቁሞ መሔድ  ብርቅ የሆነበት ዘመን ላይ ደርሰናል።

➾  ጌታ ተነሣ ስንል እኛም መነሣት አለብን።  ከከፋፋይነት መቃብር ወጥተን  አንድ የሚያደርገን  ሐሳብ  መኖር  አለበት ።

  • በቂም በቀል እና በሴራ መቃብር ውስጥ ሆነን እንኳን አደረሳችሁ ብንባባል  የውሸት የይሁዳ ሰላምታ ይሆናል ።
  • እንደ ይሁዳ በልባችን ፥ ጥላቻ ፥ ፍቅረ  ነዋይ ፥ ቂምና በቀል ፥ ተንኮል ፥ ውሸት ፥ ሐሜት ፥ ሐሰት ፥ ትውዝፍት ፥ ሱሰኝነት ፥ ጣዖትን ፥ ማምለክ ፥  ምዋርት ፥ ጥል ፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት ፥  እያለ  በምንም አይነት መንገድ  የእውነት ሰላምታ ሊሆን አይችልም ስለዚህ  ከመቃብር እንውጣ ።  ያንጊዜ ትንሣኤያችን  በግልጥ  ቅዱሳት አንስት የሚያዩት ሐዋርያት የሚመልከቱት ይሆናል። በመቃብር ሆነን ስለ ትንሣኤ ብናወራ  እውነት አይሆንም  አያምርብንም።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተነሣ እኛም  በትንሣኤ ልቡና እንነሣ። የዘረኝነት፣ የውሸት፣ የጥላቻ፥ የበቀል፣ የሐሜት፣ የከንቱ ውዳሴ፣ የትዕቢት፣ የራስ ወዳድነት መቃብርን ፈንቅለን እንውጣ  ፣ በአፋችን እንኳን አደረሳችሁ እየተባባልን በልባችን ግን ቀጣይ ዓመት እንዳንደርስ እየተገዳደን ከሆነ ግን ይሁዳነት ነው። ይሁዳ ጌታን የሸጠው በአፉ ሰላም እያለ ነው ። ሁሉም ከተንኮል፣ ከሽንገላ መቃብር ይውጣ እና የፍቅር ትንሣኤን ይነሣ። እግዚአብሔር  የፍቅር  ትንሣኤ እንድናከብር አምላካችን ያድለን።

«እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ። ፈጥናችሁም ሂዱና፡— ከሙታን ተነሣ፥ እነሆም፥ ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል በዚያም ታዩታላችሁ፥ ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሩአቸው።»  የማቴዎስ ወንጌል 28:6-7

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ!  አሜን ።

ይቆየን።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/tinsae_small_2.png 283 220 Tesfaye Zerihun https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg Tesfaye Zerihun2025-04-19 19:29:372025-04-19 19:32:13ትንሣኤ
Search Search

በቅርብ ግዜ የተለቀቁ

  • የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ
  • ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል (ህዳር) 2025
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም.
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም. — ፎቶ
  • አዲስ አመት – ፳፻፲፰ ዓ.ም.

በፌስቡክ ያግኙን

© ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም, St. George EOTC Trondheim , በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ
ኢሜይል | አጥቢያ ፖርታል
Link to: ጸሎተ ሐሙስ Link to: ጸሎተ ሐሙስ ጸሎተ ሐሙስ Link to: ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል 2025 Link to: ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል 2025 ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top