ስለ እኛ

ታሪክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  የትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መነሻው እ.ኤ.አ በ1995 መጨረሻ ላይ ለትምህርት ወደ ኖርዌይ ትሮንዳሔም በመጡ የቤተክርስቲያን ፍቅር ባላቸው ተማሪዎች አማካኝነት የተመሰረተ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። ሰንበት ት/ቤቱ በተለያዩ መዋቅሮች ተደራጅቶ አገልግሎቱን አጠናክሮ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ትሮንዳሔም ለመጡ የእምነቱ ተከታዮች አገልግሎት ዘወትር እሁድ የፀሎት መርሐግብር እንዲሁም በአበይት በዓላት ጊዜ የቅዳሴ አገልግሎት  እየሰጠ የቆየ ሲሆን እ.ኤ.አ በ2010 በኖርዌይ ሀገር በሐይማኖት ተቋምነት ተመዝግቦ ህጋዊ ሰውነት አግኝቷል። በእ.ኤ.አ በ2013 ደግሞ ወደ አጥቢያነት በማደግ ቃለዓዋዲው መሰረት አድርጎ ሰበካ ጉባዔ በማደራጀት አገልግሎቱን አስፍቶ ቀጥሏል።

በአሁኑ ወቅት አጥቢያችን ከሰበካ ጉባዔ ጀምሮ በተለያዩ መዋቅሮች ተደራጅቶ አገልግሎቱን አጠናክሮ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ትሮንዳሔም ለመጡ የእምነቱ ተከታዮች አገልግሎቱን  እየሰጠ ሲሆን ከ 200 የማያንሱ አባላት አሉት።

ከአጥቢያችን ዋነኛ አላማዎች ውስጥ አንዱ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ምዕመናንና ምዕመናት እንዲሁም የቤተክርስቲያኒቱን እምነትና ስርዓት ማወቅ ለሚፈልጉ ሁሉ በቤተክርስቲያኒቷ ዕምነትና ስርዓት መሰረት ትምህርተ ወንጌልን ማስተማር፣ ሲሆን ለዚህ አላማ መሳካት በኖርዌይ ሀገር ከሚገኙ የኢ/ኦ/ተ/ ቤ/ክርስቲያናትና ሰንበት ት/ቤቶች ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል።

የዘወትር አገልግሎት

ቅዳሴ፦ ዘወትር እሑድ እንዲሁም በበዓላት እና በንግሥ ቀን

ምህላ፦ በዐቢይ ጾም፣  እና እንደ አስፈላጊነቱ ሲታወጅ