የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ

የኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊው ክበረ በዓል ህዳር 6 እና 7 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ።

ህዳር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በልዩ ጉባኤ የተጀመረው አገልግሎት፣ በለሊቱ ማኀሌት ቀጥሎ ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም በቅዳሴ፣  በትምህርተ ወንጌል፣ በመዝሙር አገልግሎት እና በጸበል ጸዲቅ መርሐ ግብር ተጠናቋል።

በመርሐ ግብሩም የስታንቫገር ደብረ ገነት መድኃኒዓለም አስተዳዳሪ መልአከ ገነት መምህር አብርሃም፣ ቀሲስ ካሳዬ ከክርስቲያን ሳንድ፣ ቀሲስ ኃ/ማርያም ከስዊድን እና ዲያቆናት ክብረ በዓሉን በቅዳሴ እና በትምህርት ምዕመናኑን ያገለገሉ ሲሆን፣ የደብሩ ዘማሪያን ክብረ በዓሉን የተመለከተ ወረብ እና መዝሙሮች አቅርበዋል።

በደብሩ አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ቀለመወርቅ ቃለ ምህዳን ከተሰጠ በኋላ የጸበል ጸዲቅ መርሐ ግብር በማከናወን የክብረ በዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

የበዓሉን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ!