በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ እኛ
  • የፎቶ ማኅደሮች
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ቅድስት

“እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።” ኤፌሶን 5 ÷ 27

የአብይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት “ቅድስት” ተብሎ የሚጠራበት ምክንያት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት የሚከተሉት ናቸው።

  • የቅድስና ትርጉም፡ “ቅድስት” ማለት “የተቀደሰች፣ የተለየች” የከበረች ” ማለት ነው። ይህ ሳምንት በልዩ መንፈሳዊ ትኩረት እና በጸሎት፣ በጾም እና በንስሃ ስለሚታለፍ ቅድስት ተብሎ ይጠራል።
  • በዚ ሳምንት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ የጀመረው የ40 ቀን እና ሌሊት ጾም የሚታሰብበት በመሆኑ ቅድስት ይባላል።
  • ስያሜው ከኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ አስተምህሮ ነው፡፡

ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡ የቤተክርስቲያን ትምህርት፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን ታስተምርበታለች ፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤ የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ እና ወንጌላቱም ስለ ቅድስት የሚያስተምሩ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ፣ የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት “ቅድስት” ተብሎ የሚጠራው በውስጡ ባለው መንፈሳዊ ትኩረት፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ጾም ትውስታ እና በቤተክርስቲያን ትምህርት ነው።

ስለዚህ ቅድስት ሲባል የሚጠቁመን እራሳችንን ቁዱስና እና ንጹህ አድርገን በንስሐ ታጥበን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን እየተቀበልን እኔ ቅዱስ ነኘና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ እንዳለ ከሐጢአት ከበደል ከክፋት ከተንኮል ከቂም ከበቀል ከሐሜት ከሐሰት ከምቀኝነት ከዘረኝነት ወጥተን በጎ በጎውን በማሰብ መልካም ሥራ በመሥራት መንፈሳዊ ሰው በመሆን ልንኖር ይገባል ፣አምላካችን መልካሙን ሁሉ እንድናደርግ ይርዳን አሜን ፣

ይቆየን ።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/eotc-favicon.png 169 151 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2025-03-01 13:05:582025-03-01 13:06:59ቅድስት
Search Search

በቅርብ ግዜ የተለቀቁ

  • የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ
  • ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል (ህዳር) 2025
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም.
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም. — ፎቶ
  • አዲስ አመት – ፳፻፲፰ ዓ.ም.

በፌስቡክ ያግኙን

© ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም, St. George EOTC Trondheim , በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ
ኢሜይል | አጥቢያ ፖርታል
Link to: ዘወረደ Link to: ዘወረደ ዘወረደ Link to: ምኵራብ Link to: ምኵራብ ምኵራብ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top