በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ እኛ
  • የፎቶ ማኅደሮች
  • ያግኙን
  • Menu Menu

የ፳፻፲ ዓ.ም. የዘመን መለወጫና የመስቀል ደመራ በዓላት በደመቀ ሁኔታ ተከበሩ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የ፳፻፲ ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓልን በማስመልከት እሁድ ጷጉሜን ፭፥፳፻፱ ዓ.ም ከዴንማርክ ተጋብዘው በመጡት አባ ዘሚካኤል የቅዳሴ አገልግሎትና የወንጌል ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በዕለቱ ከትሮንዳሄምና አካባቢው የተገኙ ምዕመናንም በክብረ በዓሉ ላይ ታድመዋል። በተጨማሪም ቀኑን የተመለከቱ መዝሙሮችም በኅብረት ተዘምረዋል።

የመስቀል ደመራ በዓል ማክሰኞ መስከረም ፲፮፥፳፻፲ ዓ.ም በትሮንዳሔምና አካባቢው ከተገኙ ምዕመናን እንዲሁም ከቅዱስ ሚካኤል የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመጡ ምዕመናንና አገልጋዮች በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።

በዓሉ ማክሰኞ ዕለት ከሰዓት በኋላ 17:00 ሰዓት ላይ በጋራ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን ከቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመጡ አገልጋዮች ወረብና ቀኑን የሚያወሱ ንባቦች ቀርበዋል። በመቀጠልም የቅዱስ ጊዮርጊስ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መዘምራን በዓሉን የተመለከተ መዝሙራትን ያቀረቡ ሲሆን ስለመስቀል በዓል የሚያስረዳ ስነ ጽሁፍም ቀርቧል። ቀጥሎም ደመራው በወረብና በመዝሙር ምስጋና በመታጀብ ተለኩሷል። መዘምራንና መላው ምእመንም በጋራ በመዘመር በዓሉን አድምቀውት አምሽተዋል። በመጨረሻም ምእመናኑ ለበዓሉ የተዘጋጀውን ዝክር ቀምሰው ወደ የመጡበት በሰላም ተሸኝተዋል።

በዚሁ አጋጣሚ በተለያዩ መንገዶች ለዝግጅቱ መሳካት ብሎም ለበዓሉ ድምቀት መንፈሳዊ አስትዋጽኦ ላበረከታችሁ ምዕመናን ሁሉ በሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ልባዊ ምስጋናችንን ማቅረብ እንወዳለን።

የበዓላቱን አከባበር በፎቶ ይመልከቱ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/gal-newyear-meskel-09263316.jpg 360 640 tc https://eotc-trondheim.no/a/wp-content/uploads/logo-trondheim.svg tc2017-09-30 13:53:282019-02-14 21:02:58የ፳፻፲ ዓ.ም. የዘመን መለወጫና የመስቀል ደመራ በዓላት በደመቀ ሁኔታ ተከበሩ
Search Search

በቅርብ ግዜ የተለቀቁ

  • የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዳሴ ቤቱ ዓመታዊ ክብረ በዓል ህዳር ፮ እና ፯፥ ፳፻፲፰ ዓ.ም በድምቀት ተከበረ
  • ሊቀ-ሰማዕቱ-ቅዱስ-ጊዮርጊስ-ዓመታዊ-ክብረ በዓል (ህዳር) 2025
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም.
  • መስቀል – ፳፻፲፰ ዓ.ም. — ፎቶ
  • አዲስ አመት – ፳፻፲፰ ዓ.ም.

በፌስቡክ ያግኙን

© ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትሮንዳሔም, St. George EOTC Trondheim , በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ
ኢሜይል | አጥቢያ ፖርታል
Link to: የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ሚያዚያ ፳ እና ፳፩ ፥ ፳፻፱ ዓ.ም Link to: የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ሚያዚያ ፳ እና ፳፩ ፥ ፳፻፱ ዓ.ም የሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል... Link to: የ፳፻፲ ዓ.ም. የዘመን መለወጫና የመስቀል ደመራ በዓላት በደመቀ ሁኔታ ተከበሩ Link to: የ፳፻፲ ዓ.ም. የዘመን መለወጫና የመስቀል ደመራ በዓላት በደመቀ ሁኔታ ተከበሩ የ፳፻፲ ዓ.ም. የዘመን መለወጫና የመስቀል ደመራ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top