የ፫ ቀናት መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሄደ፤ የ፳፻፰ ዓ.ም ቅዱስ ዮሐንስ በዓልም በድምቀት ተከበረ

በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።

የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ።

መዝ ፷፭፥፲፩

እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ።

የቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በትሮንዳሔም ከጷግሜ ፮፥፳፻፯ ዓ.ም እስከ መስከረም ፪፥፳፻፰ ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት የቆየ መንፈሳዊ ጉባኤና የአዲስ ዓመት ክብረ በዓል ከኢትዮጵያ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተጋብዘው ወደ አውሮፓ በመጡት መምህር (ቀሲስ) ለማ በሱፍቃድ አካሄደ። በአዲስ አመት ዋዜማ በስብከተ ወንጌል የተጀመረው ጉባዔ ቅዳሜ መስከረም ፩፥፳፻፰ ዓ.ም ሲቀጥል መርሐ ግብሩ በኪዳን ተጀምሮ፣ የአመቱ ባሕረ ሃሳብ ወጥቶ ስለቤተክርስቲያናችን ዘመን አቆጣጠር ትምህርት ተሰጥቷል። የእሁድ መርሐ ግብርም እንዲሁ በኪዳን ጸሎት ተጀምሮ ትምህርት ከተሰጠ በኋላ በተለይም በዓሉን የሚያስታውሱ መዝሙሮች ተዘምረው የጉባዔው ፍጻሜ ሆኗል።

መርሃግብሩን በፎቶ ይመልከቱ