ለ፪ ቀናት የቆየ ልዩ መንፈሳዊ ጉባዔ ተካሄደ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰሜን ምዕራብ አውሮጳ ሃገረ ስብከት የትሮንዳሔም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት ከኢትዮጵያ ወደ አውሮጳ በመጡት በኩረ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ እና መጋቤ ሐዲስ ምሥጢረ ሥላሴ ማናዬ ለ፪ ቀናት የቆየ የዝማሬና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ተካሄደ። ጉባዔው ከትሮንዳሔምና አካባቢው በተገኙ ምዕመናን ቅዳሜ መስከረም ፳፰ በ 9:00 ሰዓት እንዲሁም መስከረም ፳፱ በ 10:30 ሰዓት ስለሃገራችን ሰላምና መረጋጋት የዘወትርና የምኅላ ጸሎት በማድረስ ተጀምሯል። በመቀጠልም ያሬዳዊ መዝሙሮች በበኩረ መዘምራን ኪነጥበብ ከስብከተ ወንጌል አገልግሎት በፊትና በኋላ ተዘምረዋል። የሁለቱም ቀናት የስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተሰጠው በመጋቤ ሐዲስ ምሥጢረ ሥላሴ ነበር። በተጨማሪም ስለ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ከምዕመናን የቀረቡ የተለያዩ ጥያቄዎች በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። ከመርሃግብራቱ ፍጻሜም በኋላ ምዕመናን የተዘጋጀውን ዝክር ቀምሰው ወደየመጡበት በሰላም ተሸኝተዋል።

ጉባዔውን በምስል ይመልከቱ!